ስለተጀመረው የሰላም ንግግር የማበረታቻ እና የመልካም ምኞቶች መግለጫ


ስለተጀመረው የሰላም ንግግር የማበረታቻ እና የመልካም ምኞቶች መግለጫ እኛ ስማችን ከዚህ በታች የተዘረዘረው አገር በቀል የሲቪክ ማህበራት በደቡብ አፍሪካ፣ ፕሪቶሪያ ከተማ በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት እና በሕወሓት መካከል የተጀመረውን የሰላም ንግግር የምናበረታታ እና የምንደግፍ መሆኑን እየገለጽን፤ የሰላም ንግግሩ በመጀመሩ የተሰማንን ደስታ ለመግለጽ እንወዳለን። ይህ ንግግር በሰሜን ኢትዮጵያ ያለውን ጦርነት በሰላማዊ መንገድ እልባት እንዲያገኝ መንገድ […]